ምዝገባ እና ፍቃድ መስጠት
ለብሮድካስት፣ ለበይነ መረብ እና ለህትመት መገናኛ ብዙኃን ምዝገባ እና ፍቃድ መስጠት
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ጋር ውይይት አካሄደ ፡፡
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2014 (ኢ.መ.ብ.ባ)
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር "የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ለአብሮነት እሴቶች መጠናከር" በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡
የውይይት መድረኩ ዓላማ የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን የሚያሰራጯቸው ይዘቶች በሀገራችን ተከብሮ የቆየውን የሃይማኖት መቻቻልና አብሮነት ለማጠናከር እንዲሁም በሰላም እሴቶች ግንባታ ላይ ተገቢውን ሚና እንዲጫወቱ ለማስቻል ያለመ ነው፡፡
በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ኢድሪስ እንዳሉት የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን ግብረ ገብነትን በማስተማር ትውልድን ከማነፅ በተጨማሪ የጋራ እሴቶች እንዲጠናከሩ፣ አብሮነት እና ወንድማማችነት እንዲጎለብት የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው፡፡
ስለሆነም የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን በአስተምሮታቸው አሁን ላለንበት ችግር መፍትሄ በሚያመጣ ፣ ሀገር በሚገነባና መልካም ዜጋን በሚያንፅ ጉዳይ ላይ ሊያተኩሩ ይገባል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን የአብሮነት አሴቶችን በማጠናከር እና በሰላም ግንባታ ዙሪያ ሊጫወቱት ስለሚገባው ሚና እንዲሁም የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን የህግ ማዕቀፎች የሚሉ ፅሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
በመጨረሻም ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለምዝገባ የሚየስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልተው ምዝገባ ላከናወኑ ለ23 የሃይማኖት መገናኛ ብዙኃን የምዝገባ ሰርተፊኬት የመስጠት ስነ-ስርዓት ተከናውኖ ውይይቱ ተጠናቋል።
ለብሮድካስት፣ ለበይነ መረብ እና ለህትመት መገናኛ ብዙኃን ምዝገባ እና ፍቃድ መስጠት
የመገናኛ ብዙኃን እና የማስታወቂያ ይዘት ክትትልና እና ቁጥጥር ማድረግ
ለመገናኛ ብዙኃን እና ለማስታወቂያ ዘርፍ የአቅም ግንባታ መስጠት
የዘርፉን እድገት እና ለውጥ ለማጠናከር የፖሊሲ ግብዓት የሚሆኑ ጥናቶችን መሰራት
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በማህበራዊ ሚዲያ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን የተመለከተ ሀገራዊ ሪፖርት ለህዝብ ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከምግብና መድሐኒት ባለሥልጣን ጋር በመተባበር በምግብ እና መድኃኒት ማስታወቂያዎች ላይ የመገናኛ ብዙኃን ሚና ምን መሆን አለበት በሚል ዕርሰ ጉዳይ ከመገናኛ ብዙኃን፣ከማስታወቂያ ድርጅቶች ሃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለተወጣጡ ሰልጣኞች በመሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስነ-ምግባር እና መርሆዎች እንዲሁም በሚዲያ አጠቃቀም ክህሎት ዙሪያ በሁለት ክፍል ሲሰጥ የነበረዉ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ተጠናቋል።