የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለ37ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ ጉባዔ ላበረከተው አስተዋፅኦ እውቅና አገኘ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለ37ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ ጉባዔ ላበረከተው አስተዋፅኦ እውቅና አገኘ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን 37ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ ጉባዔ ውጤታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በሚዲያው ዘርፍ ላበረከተው አስተዋፅኦ እውቅና ተሰጥቶታል ።

እውቅናው የተሰጠው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሚመራው ብሔራዊ ኮሚቴ ውስጥ በመሳተፍ ጉባዔው በስኬት እንዲካሄድ በተለያየ መስክ ጉልህ ድርሻ ለነበራቸው አካላት የምስጋና እና እውቅና መርሃ ግብር በተካሄደበት ወቅት ነው።

ባለሥልጠኑ ለጉባዔው ሽፋን ለመስጠት ለመጡ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ መገናኛ ብዙኃን እና ጋዜጠኞች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል  የ24 ሰዓት አገልግሎት በመስጠት  የ37ኛዉ  የአፍሪካ ህበረት ጉባዔ ከፍተኛ የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኝ የማድረግ ስራ መስራቱ ይታወሳል።