የንግድ ኤፍ. ኤም ሬዲዮ ብሮድካስት አገልግሎት ፈቃድ ለመስጠት የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

    የንግድ ኤፍ. ኤም ሬዲዮ ብሮድካስት አገልግሎት ፈቃድ ለመስጠት 

                         የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀጽ 30 በተሰጠው ሥልጣንና 
ተግባር መሠረት በአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ኤፍ.ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ለማቋቋም የሚፈልጉ አመልካቾችን አወዳድሮ 
ለ5 /አምስት/ አመልካቾች ፈቃድ መስጠት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሠረት:-
ፈቃድ ለመስጠት የታሰበው ብሮድካስት አገልግሎት ዓይነት፡- የኤፍ.ኤም ሬዲዮ፣
አገልግሎቱ የሚሸፍነው አካባቢ፡- አዲስ አበባ፣
ዝግጁ የሆኑት የሬዲዮ ሞገዶች፡- 92.5፣ 93.5፣ 94.5፣ 95.5 እና 96.5 (MHZ) ናቸው
የፈቃድ ሁኔታዎችና ግዴታዎች፡-
ማንኛውም ባለፈቃድ ፈቃዱን ለመውሰድ ባመለከተበት ወቅት በማመልከቻው የገለጻቸው እንዲሁምበአዋጅ ቁጥር 1238/2013
እና አዋጁን ተከትለው በሚወጡ ደንብና መመሪያዎች መሰረት በፈቃዱ ውስጥ የተመለከቱ ዝርዝር ጉዳዮች የፈቃዱ ግዴታዎች 
ሆነው ይቆጠራሉ፡፡
የማመልከቻ ማቅረቢያ ጊዜና ቦታ፡-
በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ጨረታው እስከ ሚዘጋበት የ3 ወር ጊዜ
ውስጥ ከኤግዚቢሽን ማዕከል ጀርባ ከሚገኘው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የፋይናንስ፣ ግዥ፣ ንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት
ማስተባበሪያ ቢሮ ቁጥር 101 ብር 50 (ሃምሣ ብር) በመክፈል የማመልከቻ ቅጽ ወስዳችሁ በመሙላት እና ለውድድሩ አስፈላጊ
የሆኑ ሰነዶችን ከማመልከቻ ቅጹ ጋር በማያያዝ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ተጫራቾች የፕሮጀክት ሰነዳቸውን የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው 3 ወር ጊዜ ውስጥ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
የብሮድካስት ፈቃዱ ጸንቶ የሚቆይበት ጊዜ 6 ዓመት ሲሆን የፈቃድ ዘመኑ ሲጠናቀቅ የሚታደስ ይሆናል፡፡
የማመልከቻና የፈቃድ ክፍያ መጠን፤- አመልካቹ ፈቃድ እንዲሰጠው ሲወሰን የማመልከቻ ብር 500 እና የፈቃድ ብር 75,000 
(በድምሩ ሰባ አምስት ሺህ አምስት መቶ ብር) ይከፍላል፡፡
የጨረታ ሣጥኑ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በታተመ በ91ኛው ዕለት በባለሥልጣኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከቀኑ 4፡00 ሰዓት 
ተዘግቶ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይከፈታል፡፡
ባለሥልጣኑ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-53-87-55/56/65/66 በመደወል ወይም በአካል በመቅረብ መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ


የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የተለያዩ የመኪና፣መለዋወጫ ዕቃዎች፣ ህትመት እና የሆቴል አገልግሎ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለ1 ዓመት መግዛት ይፈልጋል፡፡
  ሎት፡- 1. የመኪና፣ ጎማዎችና፣ መለዋወጫ (ስፔር) እና ጌጣጌጥ
  ሎት፡- 2. የህትመት ስራ
  ሎት፡- 3. የሆቴል አገልግሎት፡-
I የሆቴል አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሆኖ ከተቋሙ በ3 ኪ.ሜትር ርቀት የሚገኝ
1. ባለ 3 ኮኮብ
2. ባለ 4 ኮኮብ
3. ባለ 5 ኮኮብ
4. ሬስቶራንት
5. ባህላዊ ሆቴል አገልግሎት የሚስጥ
II. በአዳማ ከተማ ባለ 3 ኮኮብ
III. በቢሾፍቱ ከተማ ሪዞርት ሆቴል፡፡
በግልፅ ጨረታ አውዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሠረት ተጫርቾች መሟላት ያለባችው መረጃዎች
1.ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል ከገቢዎች ሚኒስቴር የተሰጠ ክሊራንስ ወይም የድገፍ ደብደዳቤ እና በግዥ ኤጀንሲ የተሰጠ የአቅራቢነት ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
2. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 ( አንድ መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ቫትንና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ታክሶች እንዲሁም የትራንስፖርት ዋጋ ጨምሮ መሆን አለበት፡፡ የታክስ ሁኔታ ያልተገለፀ ከሆነ የቀረበዉ ዋጋ ማንኛዉንም የመንግስት ታክስና ወጪ አካቶ እንደሞላ የቆጠራል፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (COP) ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር 5,000 ብር(አምስት ሺህ ብር) በታሸገ ኤቨንቨሎፕ አድርገዉ በቴክኒካል ኦርጅናል ሰነድ ፖስታ ውስጥ አብረው በማካተት ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
5. ተጫራቾች ይህ ጨረታ ከተጋበዙ ቀን ጀምሮ ባሉት 15 (አስራ አምስት) ተከታታይ ቀናት በኃላ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡20 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በባለስልጣኑ መ/ቤት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 101 ይከፈታል፡፡
6. ተጫራቾት የሚያቀርቡት ዋጋ ቢያንስ ጨረታዉ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ እስከ 60 ቀናት ድረስ ፀንቶ የሚሆን ይሆናል፡፡
7. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ማለትም የቴክኒካል ሰነድ ኦርጅናል ኮፒ የዋጋ ሰነድም ኦርጅናል ኮፒ ለየብቻ በፖስታ ኤንቨሎፕ ማቅረብ አለባቸው፡፡
8. ስርዝ ድልዝ ያለው የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ተቀባይነት የለውም ከጨረታም ያሰርዛል፡፡
9. የመ/ቤቱ የተሸለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
10. ሁሉም ዕቃዎችና የህትመት አገልግሎቶች ናሙና(ሳምፕል) ማቅርብ ይኖርባቸዋል፡፡
 ለቴክኒክ ብቁ ከሆነ ፋይናንሻል በማወዳደር አሸናፊ ይለያል፡፡
አድራሻ፡-ቦሌ መንገድ ፍላሚንጎዳ ኤግዚቪሽን ማዕከል ጀርባ በሚያስገባው መንገድ
      ስልክ ቁጥር 0115538762